ለሁሉም ተመጣጣኝ ዋጋ ያለዉ የመብራት የዉሃ አና የጋስ  አገልግሎቶች

ሁሉም የዋሽንግተን ነዋሪዎች እንደ ኤሌክትሪክ እና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን የመሳሰሉ የዕለት ተዕለት ፍላጎቶቻቸውን ማሟላት መቻል አለባቸው። ነገር ግን በዲስትሪክቱ ውስጥ የሚገኙ ሰራተኞች የፔፕኮ (Pepco) እና የሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶች ክፍያ በከፍተኛ ሁኔታ ሲጨምር ተመልክተዋል፤ የአንዳንዶቹ ወጪ ደግሞ በቅርብ ወራት ውስጥ በእጥፍ ወይም በሶስት እጥፍ አድጓል።”

ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዳታ ሴንተሮች የሚመጣው ከፍተኛ ፍላጎት እና ውጤታማ ያልሆነ የመሰረተ ልማት አውታር ለከፍተኛ ወጪ አስተዋፅኦ አድርገዋል። ነገር ግን ሌላው ጉልህ ምክንያት ዲሲ በፔፕኮ (Pepco) ላይ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለመቻሉ ነው፤ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አመታት በእያንዳንዱ አመት ክፍያዉን ጨምሯል፣ ይህም ከሌሎች ከተሞች እና ግዛቶች በበለጠ ፍጥነት ነው። ይህ ገንዘብ በዲሲ ነዋሪዎች ኪስ ውስጥ መሆን የነበረበት እንጂ በፔፕኮ ባለሀብቶች ዘንድ መሆን የለበትም። ሰሞኑን ፍርድ ቤቶች የዲሲ የህዝብ አገልግሎት ኮሚሽን (DC’s Public Service Commission) የፔፕኮ የፍጆታ ዋጋ ጭማሪን ሲያጸድቅ የእኛን ጥቅም ባለማስጠበቁ ተጠያቂ መሆኑን ወስነዋል።

እንደ ከንቲባ፣ ጃኒስ ወጪያችንን በነዚህ መንገዶች ትቀንሳለች፦

  • የዋሽንግተን ነዋሪዎችን ከፔፕኮ (Pepco) እና ከዋሽንግተን ጋዝ (Washington Gas) የክፍያ ጭማሪ መቆጣጠር።
  • የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዳታ ማዕከላትን ተጠያቂ ማድረግ
  • ተመጣጣኝ የኃይል መሣሪያዎችን የማግኘት ዕድልን ማሳደግ
  • አርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች የኃይል ድጋፍ ለማግኘት የሚገጥሙ እንቅፋቶችን ማስወገድ
  • የመብራት ኃይል ማጭበርበርን እና ብዝበዛን ማስቆም

ለሁሉም ተመጣጣኝ የፍጆታ አገልግሎቶች የተሰኘውን ቪዲዮ ይመልከቱ

ሰዎችን ቅድሚያ የሚሰጥ መድረክ