ለዲሲ ዘብ ይቁሙ
ዲሲ ጥቃት እየተሰነዘረባት ነው፤ በዚህ ወቅት የሚያስፈልጉን ደግሞ ግፍ ሲፈጸም የሚያፈገፍጉ ሳይሆን፣ በፅናት ቆመው የሚታገሉ መሪዎች ናቸው። ይህም የሚጀምረው ጃኒስ የፖሊስ መኮንኖቻችን ከኢሚግሬሽን እና ድንበር አስከባሪ (ICE) ጋር እንዲተባበሩ፣ መረጃ እንዲለዋወጡ እና ሰዎችን አሳልፈው እንዲሰጡ የሚፈቅደውን የዲሲ ፖሊስ መመሪያን በመሻር ይሆናል። ጃኒስ የማህበረሰባችንን መብቶች እና እሴቶች ለማስከበር በአካባቢ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ጥምረት ለመፍጠር ያሉንን መሳሪያዎች ሁሉ ትጠቀማለች። የዲሲን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት (Home Rule) ለመጠበቅ ከዲሲ ተወካይ እና ከዋና አቃቤ ህግ ብራያን ሽዋልብ ጋር በቅንጅት ትሰራለች። የዲሲን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ለማስጠበቅ እና ዲሲን የሀገሪቱ 51ኛ ግዛት ለማድረግ (DC Statehood) ብቸኛው መንገድ እሱ በመሆኑ፣ ራሷ በኮንግረስ አዳራሾች በመገኘት በሁለቱም የፖለቲካ ወገኖች መካከል ጠንካራ ግንኙነት ትገነባለች።