ዲሲ ለሁሉም መሥራት አለበት
ጃኒስን ተዋወቁ
የዩንየን ፖስታ ሰራተኛ ልጅ የሆነችው ጃኒስ ሉዊስ ጆርጅ በዋርድ 4 ያደገች የሶስተኛ ትውልድ ዋሽንግተናዊት ናት። አሁን ላይ የዚሁ ዋርድ የምክር አባል ሆና የምታገለግል ሲሆን፣ ከባሏ ካይል እና ከልጇ ፒርስ ጋር እዚያው ትኖራለች። ጃኒስ በዲሲ ያሉ ሰራተኛ ቤተሰቦች ምን አይነት ፈተና እንደሚገጥማቸው በራሷ ህይወት ስለምታውቅ ፈተናዎችን ለመካላከል ትታገላቸዋለች። ከሰራተኛው ወገን በመቆም ዲሲን ደህንነቷ የተጠበቀ፣ ኑሮ ተመጣጣኝ እና መንግስት በሁሉም ስምንቱ ዋርዶች ለሚኖሩ ነዋሪዎች የሚሰራባት ከተማ ለማድረግ እንደ ከንቲባነቷ ጥረቷን ትቀጥላለች።
ሰዉን የሚያስቀድም መድረክ
ጃኒዝ ሉዊስ ጆርጅ በሁሉም 8ቱ የዲስትሪክቱ ወረዳዎች ለሚኖሩ ነዋሪዎች የሚሰራ መንግስት በመፍጠር ዲሲን ደህንነቱ የተጠበቀ እና ኑሮው ተመጣጣኝ እንዲሆን ለማድረግ ለከንቲባነት እየተወዳደሩ ነው።