Economic Development for a Thriving DC
ዲሲ ነዋሪዎች የሥራ መስክ የሚገነቡበት፣ ቤተሰብ የሚያፈሩበት እና የማህበረሰቡ አካል የሚሆኑበት ተመራጭ ከተማ መሆን አለባት። ከተማችን ለሥራ ወደዚህ ለሚመላለሱ ሰዎችና ለአሠሪዎቻቸው ብቻ ሳይሆን እዚሁ ለሚኖሩ ሰዎችም የምትመች መሆን ይኖርባታል። ጃኒስ ከንቲባ ስትሆን ይህንን የከተማችንን ራዕይ ዕውን ለማድረግ ገንዘብ መድባ ተሰራበታለች። እሷም፦
የኢኮኖሚ ልዩነቶችን መፍታት።
- በወረዳ 5፣ 7 እና 8 የግሮሰሪ ሱቆችን እና የችርቻሮ ንግድን መገንባት ቅድሚያ ይስጡ።
- በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ በሚገኙ ሰፈሮች ለሚገኙ አነስተኛ የንግድ ተቋማት የኪራይ ድጎማ ያድርጉ። ለሥራ አጥ ዜጎች ድጋፍ ይስጡ።
የከተማ መሃልን ለሁሉም ሰው የሚሆን የበለጸገ ቦታ አድርጎ እንደገና ማሰብ።
- ዋስትና የማውጣት ሥልጣን ያለው የከተማ መሃል ልማት መስሪያ ቤትን ማቋቋም እና የተላያዩ አጠቃቀም ያላቸውን ግንባታዎች ማበረታታት፤ የቢሮ ቦታዎችን በመቀነስ የመኖሪያ ቤቶችን መጨመር።
- የዲሲ (DC) ባለቤትነት ያላቸውን እና ክፍት ቦታዎችን ለጊዜያዊ መሸጫዎች (pop-ups)፣ ንግድን ማበረታቻ (incubators) እና ለአነስተኛ ንግዶች መገልገያነት ይጠቀሙ።
- በእግር የመጓዝ ምቾትን የሚያመቻቹ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቶችን ማቀናጀት።
የዩኒቨርሲቲዎችን እና የሆስፒታሎችን የኢኮኖሚ አቅም መጠቀም።
- ከዋና ዋና የዲሲ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የፈጠራ ማዕከላትን እና ዓለም አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መገኛን መገንባት፤ ይህም የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራል።
- የጤና ማሻሻያ አዲስ ግኝቶችን ፕሮግራም ከአካባቢ ሆስፒታሎች ጋር በመተባበር ማበልጸግ።
- የዩኒቨርሲቲ-ተኮር የጡረታ ማህበረሰቦችን በማስተዋወቅ አዛውንቶችን መሳብ።
ዩኒየን ስቴሽንን የምስራቅ የባህር ዳርቻ ቀዳሚ የመጎጎዣ ማዕከል ማድረግ።
- የዩኒየን ስቴሽን መልሶ ማልማትን ማጠናቀቅ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የስራ እድሎችን መፍጠር እና በትራንስፖርት አማራጮች ዙሪያ ያተኮረ የመኖሪያ ቤት ልማትን ማበረታታት።